በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በራያ አላማጣ ወረዳ አዋሳኝ ግጭት አስተዳደሩ እና የትግራይ ክልል ተካሰሱ


 በራያ አላማጣ ወረዳ አዋሳኝ ግጭት አስተዳደሩ እና የትግራይ ክልል ተካሰሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:29 0:00

በራያ አላማጣ ወረዳ አዋሳኝ ግጭት አስተዳደሩ እና የትግራይ ክልል ተካሰሱ

የትግራይ ክልል ታጣቂ ኀይሎች ወደ ራያ አላማጣ ወረዳ በመግባት አንድ ቀበሌ መቆጣጠራቸውን፣ የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አስታወቁ።

ከንቲባው ኀይሉ አበራ፣ ታጣቂዎቹ በቀበሌዋ የሚገኙትን ጎጦች ለመቆጣጠር ወሰዱት ባሉት ጥቃት ሲቪሎች መገደላቸውን፣ የአካል ጉዳት መድረሱንና ተቋማት መዘረፋቸውን ተናግረዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ረዳኢ ኃለፎም በበኩላቸው፣ ውንጀላውን አስተባብለዋል፤ በአንጻሩ ከራያ አላማጣ ወረዳ በኩል ትንኮሳ ተፈጽሞ እንደነበርና እርሱንም መመከት እንደተቻለ፣ ለአሜሪካ ድምፅ አስታውቀዋል።

ሁለቱም አካላት፣ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዳይተገበር ፍላጎት አላቸው፤ በሚል እርስ በርስ ይካሰሳሉ፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

መድረክ / ፎረም

XS
SM
MD
LG